የሀዘን መግለጫ

የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ የጉማራ- ናበጋ- ማክሰኝት ሎት 2 ፕሮጀክት ሀላፊ የነበሩት አቶ አሰፋ ስንሻው በደረሰባቸው ድንገተኛ አደጋ ህይወታቸው በማለፉ ኤጀንሲው የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።

 ለቤተሰቦቹ፣ ለጓደኞቹና ለስራ ባልደረቦቹ መፅናናትን ይመኛል።