አለም አቀፍ የሴቶች ቀን
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ እና የመንገድ ቢሮ ሴት ሰራተኞች አለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በፓናል ውይይት አከበሩ።
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲና የመንገድ ቢሮ ሴት ሰራተኞች ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል በሚል መሪ ቃል አለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በፓናል ውይይት አክብረዋል።
በፓናል ውይይቱ እንደተገለፀው በዚህ አመት የሚከበረው የሴቶች ቀን በአገር አቀፍ ደረጃ ለ49ኛ ጊዜ በክልል ደረጃ ደግሞ ለ30ኛ ጊዜ እንደሚከበርና ሞዴል የሴቶች የልማት ህብረቶችን ማጠናከር፣ ሴቶች የቁጠባ ባህላቸውን እንዲያዳብሩ በንቅናቄ እንዲቆጥቡ ማድረግ፣ በግብርናና በኢንዱስትሪ መስክ ተሰማርተው የሚገኙ ሴቶች ምርትና አገልግሎታቸውን እንዲያስተዋውቁ ማድረግ፣ ሴቶች የማህፀን በርና የጡት ጫፍ ካንሰር ቅድመ ምርመራ እንዲያደርጉ በማድረግና ቦንድ በመግዛት ለህዳሴ ግድቡ መጠናቀቅ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ ማድረግ ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተመላክቷል።
በውይይቱም ሴቶች የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ለመፍታት በጋራ ሰብሰብ ብሎ መደራጀትና ችግሮችን በውይይት የመፍታት ባህል ማዳበር እንደሚገባቸው ተገልጿል።
በውይይቱም የክልሉ መንገድ ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ጋሻው አወቀ፣ የሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ፣ የገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ቀለሙ ሙሉነህ እና ሌሎች የመንገድ ቢሮ እና የሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ አመራሮች ተገኝተዋል።
የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት የጠቅላላ ርዝመቱ 57%(ፐርሰንት) የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፤ በበጀት ዓመቱ የተለያዬ መጠን ያላቸዉ ስትራክቸሮች ግንባታም እየተከናወነ ነዉ፡፡
የአማራ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ በተያዘዉ በጀት ዓመት ለአነስተኛ፣መካከለኛ እና ትላልቅ ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም ለቱቦ ቀበራ ሥራዎች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት የስትራክቸር ግንባታ ከሚከናወንባቸዉ ፕሮጀቶች መካከል በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ የሚገኘዉ እና 52 ኪ.ሜ ርዝመት ያለዉ የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት አንዱ ነዉ፡፡
የመካነብርሃን -ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በ2012 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ በተከናወነዉ ግንባታ የጠቅላላ ርዝመቱ 57.8% የሚሆነዉ የግንባታ ሥራ ተጠናቋል፡፡ፕሮጀክቱ በተያዘዉ በጀት ዓመት ከክልሉ መንግስት በተመደበ ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት ከ4 እስከ 15 ሜትር ርዝመት ያላቸዉ 3/ሦሥት/ አነስተኛ እና መካከለኛ ድልድዮች ግንባታ እንዲሁም የቱቦ ቀበራ ሥራዎችን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ ሲሆን እስከ መጋቢት አጋማሽ 2018 ዓ.ም ድረስ በተከናወነዉ የግንባታ ሥራ የአንድ አነስተኛ ድልድይ ግንባታ ተጠናቋል፡፡ የ2 /ሁለት/ አነስተኛ እና መካከለኛ ድልድዮች ግንባታ ደግሞ የግንባታቸዉ 65% እና 20% ተከናዉኗል፡፡በ4/አራት/ ቦታዎች የሚከናወን የቱቦ ቀበራ ሥራም ተጠናቋል፡፡
የመካነብርሃን-ዋሰል መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በክልሉ በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ የሚገኙ እና በመንገድ ያልተገናኙ 7/ሰባት/ ቀበሌዎችን ርዕስ በርስ እና ከዋና መንገድ ጋር በማገናኘት የአካባቢዉን ህብረተሰብ የሚያጋጥሙ ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና አስተዳደራዊ ችግሮች እንዲፈቱ በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡

